ከጉድጓድ ውሃ ውስጥ ብረት እና ማንጋኒዝን የማስወገጃ መንገዶች
በኢትዮጵያ ከሚቆፈሩት ጥልቅ የጉድጓድ ውሃዎች ውስጥ ከ73% በላይ የሚሆኑት ከፍተኛ የብረት (Iron) እና የማንጋኒዝ (Manganese) ክምችት ይገኝባቸዋል። በኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የወጣው አስገዳጅ ብሄራዊ መስፈርት (CES 58) በመጠጥ ውሃ ውስጥ ሊኖር የሚችለውን ከፍተኛ የብረት መጠን 0.3 mg/L እንዲሁም የማንጋኒዝ መጠንን 0.1 mg/L አድርጎ ገድቧል። ነገር ግን በተግባር በተደረጉ ጥናቶች በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የብረት መጠን እስከ 4.8 mg/L እና የማንጋኒዝ መጠን እስከ 1.2 mg/...